Posts

Showing posts from July, 2024

የዳግም ውልደት እውነታዎች

 ➙“እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።” (ዮሐ 3፥3) መፅሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ዳግም ውልደት አያስተምርም። በተለምዶ የሰማነው ጌታን ስንቀበል የሰው መንፈስ ዳግመኛ እንደሚወለድ ነው። ነገር ግን  አዲስ መንፈስ የሚወለደው የመጀመሪያው መንፈስ የት ሄዶ ነው? እውነታው ይህ ነው መንፈስ ኢመዋቲ (የማይሞት) ነው። መንፈስ አይበላሽም፣ አይረክስም እንዲሁም ዳግምም አይወለድም። አንዴ ይወለዳል ለዘለዓለም ከፍታውን ጠብቆ ይኖራል። ሁሉም ሰው በምድር ከእናቱ ማህፀን ከመወለዱ በፊት ከእግዚአብሔር መንፈሱ ተወልዷል። መንፈስ ሰው ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊትም ነበር ሰው ከምድር በስጋ ሞቶ ሲለይም ይኖራል። በመሆኑም መንፈስ ስለማይጠፋ እና ስለማይመት የመንፈስ ዳግም መወለድ የሚባል ነገር የለም። ዳግመኛ የሚወለደው የሰው ነፍስ ነው። በነፍስህ ዳግመኛ የምትወለደው መንግስተ ሰማይ ለመግባትአይደለም። ነገር ግን ከዚህ አለም ክፋት አምልጠህ የእግዚአብሔርን ህይወት እዚሁ ምድር ላይ መኖር እንድትጀምር ነው። ለመንፈስ ዳግም መወለድ ትምህር ጥቅም ላይ የሚውለው ዋና ሀሳብ ዮሐንስ ምዕራፍ 3 ነው።ነገር ግሉ ቃል ስለ ዳግም መወለድ አይናገርም። በዮሐንስ 3:3 ላይ "ዳግመኛ ካልተወለደ " ተብሎ የተተረጎመው የአራማይክ ቃል "አኖቴን-ጌኖ"  (ánōthen gennáō) የሚል ሲሆን ትክክለኛ ትርጉሙ "ከላይ ካልተወለደ" ማለት ነው። ኢየሱስ "ከላይ" ያልተወለደ ሰው የእግዚአብሔር መንግስት ሊያይ አይችልም እያለ ነው። ወይም የእግዚአብሔር መንግስት የሚያየው ቀድሞ ከላይ (እግዚአብሔር) የተወለደ ሰው ብቻ ነው እያለ ነው። ዮሐንስ 3 ስለ መንፈስ የመጀመሪያ ው...